ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

2 ሳሙኤል 22:3-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. አምላኬ፣ የምጠጋበት ዐለቴ፣ጋሻዬና የድነቴ ቀንድ ነው።እርሱም ጠንካራ ምሽጌ፣ መጠጊያና አዳኜ ነው፤ከኀይለኞች ሰዎች ታድነኛለህ።

4. ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሔርንእጠራለሁ፤ ከጠላቶቼም እድናለሁ።

5. “የሞት ማዕበል ከበበኝ፤የጥፋትም ጐርፍ አሰጠመኝ።

6. የሲኦል ገመድ ተጠመጠመብኝ፤የሞትም ወጥመድ ተጋረጠብኝ።

7. በጨነቀኝ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤ወደ አምላኬም ጮኽሁ።እርሱም ከመቅደሱ ድምፄን ሰማ፤ጩኸቴም ከጆሮው ደረሰ።

8. “ምድር ተንቀጠቀጠች፤ ተናወጠችም፤የሰማያትም መሠረቶች ተናጉ፤እርሱ ተቈጥቶአልና ራዱ።

9. ከአፍንጫው የቊጣ ጢስ ወጣ፤ከአፉ የሚባላ እሳት ነደደ፤ከውስጡም ፍሙ ጋለ።

10. ሰማያትን ሰንጥቆ ወረደ፤ከእግሩም በታች ጥቅጥቅ ያለ ደመና ነበረ።

11. በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ፤በነፋስም ክንፍ መጠቀ።

12. ጨለማው በዙሪያው እንዲከበው፣ጥቅጥቅ ያለውም የሰማይ ዝናም ደመና እንዲሰውረው አደረገ።

13. በእርሱ ፊት ካለው ብርሃን፣የመብረቅ ብልጭታ ወጣ።

14. እግዚአብሔር ከሰማያት አንጐደጐደ፤የልዑልም ድምፅ አስተጋባ።

15. ፍላጻውን ሰድዶ ጠላቶቹን በተናቸው፤መብረቆቹንም ልኮ አወካቸው።

16. ከእግዚአብሔር ተግሣጽ፣ ከአፍንጫውከሚወጣው፣ ከእስትንፋሱ ቍጣ የተነሣ፣የባሕር ሸለቆዎች ታዩ፤ የምድርመሠረቶችም ተገለጡ።

17. “ከላይ እጁን ዘርግቶ ያዘኝ፤ከጥልቅ ውሆችም ውስጥ አወጣኝ።

18. ከብርቱ ጠላቶቼ፣ከማልቋቋማቸውም ባለጋሮቼ ታደገኝ።

19. በመከራዬ ቀን መጡብኝ፤ እግዚአብሔር ግን ደገፈኝ።

20. ሰፊ ወደ ሆነ ስፍራ አወጣኝ፤በእኔ ደስ ስለ ተሰኘም አዳነኝ።

21. “እግዚአብሔር እንደ ጽድቄ መለሰልኝ፤እንደ እጄም ንጹሕነት ብድራትን ከፈለኝ፤

22. የእግዚአብሔርን መንገድ ጠብቄአለሁና፤ከአምላኬም ዘወር ብዬ ክፉ ነገር አላደረግሁም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 2 ሳሙኤል 22