ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 7:16-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. የሚኪር ሚስት መዓካ ወንድ ልጅ ወለደች፤ ስሙንም ፋሬስ አለችው። የወንድሙም ስም ሱሮስ ይባላል፤ ወንዶች ልጆቹም ኡላምና ራቄም ነበሩ።

17. የኡላም ወንድ ልጅ፤ባዳን፤እነዚህ የምናሴ ልጅ፣ የማኪር ልጅ፣ የገለዓድ ወንዶች ልጆች ናቸው፤

18. እኅቱ መለኬት ኢሱድን፣ አቢዔዝርንና መሕላን ወለደች።

19. የሸሚዳ ወንዶች ልጆች ደግሞ እነዚህ ነበሩ፤አሒያን፣ ሴኬም፣ ሊቅሒ፣ አኒዓም።

20. የኤፍሬም ዘሮች፤ሹቱላ፣ ልጁ ባሬድ፣ልጁ ታሐት፣ ልጁ ኤልዓዳ፣ልጁ ታሐት፣

21. ልጁ ዛባድ፣ልጁ ሹቱላ።ኤድርና ኤልዓድ ከብቶች ለመስረቅ በወረዱ ጊዜ፣ የአገሩ ተወላጆች በሆኑት በጌት ሰዎች ተገደሉ።

22. አባታቸውም ኤፍሬም ብዙ ቀን አለቀሰላቸው፤ ዘመዶቹም መጥተው አጽናኑት።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 7