ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 6:63-69 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

63. ለሜራሪ ዘሮች በየጐሣቸው ከሮቤል፣ ከጋድና ከዛብሎን ድርሻ ላይ ዐሥራ ሁለት ከተሞች ተመደቡላቸው።

64. እስራኤላውያንም ከተሞቹን በዚሁ ሁኔታ መድበው ከነመሰማሪያዎቻቸው ለሌዋውያኑ ሰጧቸው።

65. ቀደም ብለው የተጠቀሱትንም ከተሞች ከይሁዳ፣ ከስምዖንና ከብንያም ነገድ ላይ ወስደው መደቡላቸው።

66. ለአንዳንድ የቀዓት ጐሣዎችም ከኤፍሬም ነገድ ድርሻ ላይ የሚኖሩበት ቦታ ተሰጣቸው።

67. በኰረብታማው በኤፍሬም ምድር የሚገኙትን የመማፀኛ ከተሞች ሴኬምን፣ ጌዝርን፣

68. ዮቅምዓምን፣ ቤትሖሮን፣

69. ኤሎንንና ጋትሪሞን ከነመሰማሪያዎቻቸው ሰጧቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 6