ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 6:11-25 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

11. ዓዛርያስ አማርያን ወለደ፤አማርያም አኪጦብን ወለደ፤

12. አኪጦብ ሳዶቅን ወለደ፤ሳዶቅ ሰሎምን ወለደ፤

13. ሰሎም ኬልቅያስን ወለደ፤ኬልቅያስ ዓዛርያስን ወለደ፤

14. ዓዛርያስ ሠራያን ወለደ፤ሠራያ ኢዮሴዴቅን ወለደ።

15. እግዚአብሔር የይሁዳና የኢየሩሳሌም ሕዝብ በናቡከደነፆር እጅ ተማርከው እንዲወሰዱ ባደረገ ጊዜ ኢዮሴዴቅም አብሮ ተማርኮ ሄደ።

16. የሌዊ ወንዶች ልጆች፤ጌድሶን፣ ቀዓት፣ ሜራሪ።

17. የጌድሶን ወንዶች ልጆች፤ሎቤኒ፣ ሰሜኢ።

18. የቀሃት ወንዶች ልጆች፤እምበረም፣ ይስዓር፣ ኬብሮን፣ ዑዝኤል።

19. የሜራሪ ወንዶች ልጆች፤ሞሖሊ፣ ሙሲ።በየአባቶቻቸው ቤተ ሰብ የተቈጠሩት የሌዊ ጐሣዎች የሚከተሉት ናቸው፤

20. ከጌርሶን፤ልጁ ሎቤኒ፣ ልጁ ኢኤት፣ልጁ ዛማት፣

21. ልጁ ዮአክ፣ልጁ አዶ፣ ልጁ ዛራ፣ ልጁ ያትራይ።

22. የቀዓት ዘሮች፤ልጁ አሚናዳብ፣ ልጁ ቆሬ፣ልጁ አሴር፣

23. ልጁ ሕልቃና፣ልጁ አቢሳፍ፣ ልጁ አሴር፣

24. ልጁ ኢኢት፣ ልጁ ኡርኤል፣ልጁ ዖዝያ፣ ልጁ ሳውል።

25. የሕልቃና ዘሮች፤አማሢ፣ አኪሞት።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 6