ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 26:1-5 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. የቤተ መቅደሱ በር ጠባቂዎች አመዳደብ፤ከቆሬያውያን ወገን፤ ከአሳፍ ወንዶች ልጆች አንዱ የሆነው የቆሬ ወንድ ልጅ ሜሱላም።

2. ሜሱላም ወንዶች ልጆች ነበሩት፤የመጀመሪያው ዘካሪያስ፣ሁለተኛው ይዲኤል፣ሦስተኛው ዮዛባት፣አራተኛው የትኒኤል፣

3. አምስተኛው ኤላም፣ስድስተኛው ይሆሐናን፣ሰባተኛው ኤሊሆዔናይ።

4. ዖቤድኤዶምም እንደዚሁ ወንዶችልጆች ነበሩት፤የመጀመሪያው ሸማያ፣ሁለተኛው ዮዛባት፣ሦስተኛው ኢዮአስ፣አራተኛው ሣካር፣አምስተኛው ናትናኤል፣

5. ስድስተኛው ዓሚኤል፣ሰባተኛው ይሳኮር፣ስምንተኛው ፒላቲ፤እግዚአብሔር ዖቤድኤዶምን ባርኮታልና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 26