ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 24:15-26 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. ዐሥራ ሰባተኛው ለኤዚር፣ዐሥራ ስምንተኛው ለሃፊጼጽ፣

16. ዐሥራ ዘጠነኛው ለፈታያ፣ሃያኛው ለኤዜቄል፣

17. ሃያ አንደኛው ለያኪን፣ሃያ ሁለተኛው ለጋሙል፣

18. ሃያ ሦስተኛው ለድላያ፣ሃያ አራተኛ ለመዓዝያ ወጣ።

19. የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ባዘዘውና ከቀድሞ አባታቸው ከአሮን በተሰጣቸው መመሪያ መሠረት ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በሚገቡበት ጊዜ፣ የተወሰነላቸው ሥርዐት ይህ ነበር።

20. ከቀሩት የሌዊ ዘሮች ደግሞ፦ከእንበረም ወንዶች ልጆች፤ ሱባኤል፤ከሱባኤል ወንዶች ልጆች፤ ዬሕድያ።

21. ከረዓብያ ወንዶች ልጆች፤አለቃው ይሺያ።

22. ከይስዓራውያን ወገን፤ ሰሎሚትከሰሎሚት ወንዶች ልጆች፤ ያሐት።

23. የኬብሮን ወንዶች ልጆች፤ የመጀመሪያው ይሪያ፣ ሁለተኛው አማርያ፣ ሦስተኛው የሕዚኤል፣ አራተኛው ይቀምዓም።

24. የዑዝኤል ልጅ፤ ሚካ።ከሚካ ወንዶች ልጆች ሻሚር።

25. የሚካ ወንድም ይሺያ፤ከይሺያ ወንዶች ልጆች ዘካርያስ።

26. የሜራሪ ወንዶች ልጆች፤ ሞሖሊ፣ ሙሲ።የያዝያ ወንድ ልጅ በኖ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 24