ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ነገሥት 3:15-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. ሰሎሞንም ከእንቅልፉ ነቃ፤ እነሆ ሕልም መሆኑን ተረዳ።ከዚያም ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሶ፣ በጌታ ኪዳን ታቦት ፊት ቆመ፤ የሚቃጠል መሥዋዕትና የኅብረት መሥዋዕት አቀረበ፤ ለሹማምቱም ሁሉ ግብዣ አደረገ።

16. በዚህን ጊዜ ሁለት ዝሙት አዳሪዎች ወደ ንጉሡ መጥተው ከፊቱ ቆሙ።

17. ከእነርሱም አንዲቱ እንዲህ አለች፣ “ጌታዬ ሆይ፤ ይህች ሴትና እኔ በአንድ ቤት አብረን እንኖራለን፤ አብራኝ እያለችም እኔ ልጅ ወለድሁ፤

18. እኔ ከወለድሁ ከሦስት ቀን በኋላም፣ ይህች ሴት ወለደች፤ ያለ ነው እኛ ብቻ ነን፤ ከሁለታችን በቀር በዚያ ቤት ማንም አልነበረም።

19. “የዚህች ሴት ሕፃን ልጅ ስለ ተኛችበት ሌሊት ሞተ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ነገሥት 3