ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ነገሥት 18:41-46 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

41. ኤልያስም አክዓብን፣ “የከባድ ዝናብ ድምፅ ይሰማልና ሂድና ብላ፤ ጠጣም” አለው።

42. ስለዚህ አክዓብ ሊበላና ሊጠጣ ሄደ፤ ኤልያስ ግን ወደ ቀርሜሎስ ተራራ ጫፍ ወጣ፤ ፊቱንም በጒልበቶቹ መካከል አድርጎ ወደ መሬት አቀረቀረ።

43. አገልጋዩንም፣ “ውጣና ወደ ባሕሩ ተመልከት” አለው።አገልጋዩም ሄዶ ተመለከተና፤ “በዚያ ምንም የለም” አለው።ኤልያስ ሰባት ጊዜ፣ “እንደ ገና ሂድ” አለው።

44. በሰባተኛው ጊዜ አገልጋዩ፣ “እነሆ፤ የሰው እጅ የምታህል ትንሽ ደመና ከባሕሩ እየወጣች ነው” አለው።ኤልያስም፣ “ሂድና አክዓብን፣ ‘ዝናቡ ሳያግድህ፣ ሠረገላህን ጭነህ ውረድ’ ብለህ ንገረው” አለው።

45. ወዲያውኑም ሰማዩ በጥቊር ደመና ተሸፈነ፤ ነፋሱ ነፈሰ፤ ከባድ ዝናብ ጣለ፤ አክዓብም በሠረገላ ተቀምጦ ወደ ኢይዝራኤል ሄደ።

46. የእግዚአብሔርም ኀይል በኤልያስ ላይ ወረደ፤ ኤልያስም ልብሱን ከፍ አድርጎ በቀበቶው ካጠበቀ በኋላ እስከ ኢይዝራኤል ድረስ አክዓብን ቀድሞት ሮጠ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ነገሥት 18