ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ሳሙኤል 18:7-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ሴቶቹም እንዲህ ሲሉ በመቀባበል ዘፈኑ፤“ሳኦል ሺህ ገደለ፤ዳዊት ግን ዐሥር ሺህ ገደለ።”

8. ሳኦል እጅግ ተቈጣ፤ ይህም ነገር አላስደሰተውም። እርሱም፣ “ለዳዊት ዐሥር ሺህ አሉለት፤ ለእኔ ግን ሺህ ብቻ! እንግዲህ መንግሥት እንጂ ሌላ ምን ቀረው” አለ።

9. ከዚያች ዕለት አንሥቶ ሳኦል ዳዊትን በቅናት ዐይን ይመለከተው ጀመር።

10. በማግስቱም ከእግዚአብሔር የታዘዘ ክፉ መንፈስ በሳኦል ላይ በኀይል መጣበት፣ በዚህ ጊዜ ዳዊት ወትሮ እንደሚያደርገው ሁሉ በገና ሲደረድር፣ ሳኦል በቤቱ ሆኖ ትንቢት ይናገር ነበር። ሳኦል በእጁ ጦር ይዞ ነበር፤

11. እርሱም፣ “ዳዊትን ከግድግዳው ጋር አጣብቀዋለሁ” ብሎ በማሰብ ጦሩን ወረወረበት፤ ዳዊት ግን ሁለት ጊዜ ከፊቱ ዘወር አለ።

12. እግዚአብሔር ከእርሱ ተለይቶ ከዳዊት ጋር ስለ ሆነ፣ ሳኦል ዳዊትን ፈራው።

13. ስለዚህ ዳዊትን ከአጠገቡ በማራቅ የሺህ አለቃ አደረገው። ዳዊትም ሰራዊቱን እየመራ በፊታቸው ይወጣና ይገባ ነበር።

14. እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለ ነበር የሚያደርገው ነገር ሁሉ ይሳካለት ነበር።

15. ሳኦልም፣ ዳዊት እንደ ተሳካለት ባየ ጊዜ ፈራው፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ሳሙኤል 18