ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ሳሙኤል 18:6-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ዳዊት ፍልስጥኤማዊውን ከገደለ በኋላ፣ ሰዎቹ ወደየቤታቸው በሚመለሱበት ጊዜ፣ ሴቶች ከበሮና መሰንቆ ይዘው እየዘፈኑ፣ እየጨፈሩና እልል እያሉ ንጉሥ ሳኦልን ለመቀበል ከእስራኤል ከተሞች ሁሉ ወጡ።

7. ሴቶቹም እንዲህ ሲሉ በመቀባበል ዘፈኑ፤“ሳኦል ሺህ ገደለ፤ዳዊት ግን ዐሥር ሺህ ገደለ።”

8. ሳኦል እጅግ ተቈጣ፤ ይህም ነገር አላስደሰተውም። እርሱም፣ “ለዳዊት ዐሥር ሺህ አሉለት፤ ለእኔ ግን ሺህ ብቻ! እንግዲህ መንግሥት እንጂ ሌላ ምን ቀረው” አለ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ሳሙኤል 18